አለማወቅ አጠፋት ያልናትን አለም ማወቃችን
አላዳናትም። ባለማወቅ ማወቃችን ጠላታችን
እስኪሆን ድረስ ተራቀቅን። በዚህም ጦርነቶቻችን እንዲሁ የሚያልፉ ብቻ ሳይሆኑ ቀሩ። ጦሮቻችን ሰው ብቻ ሳይሆን ሀገርም ፈርሶ እስኪቀር ድረስ ሀይልን አግኝተውልና “ወዮ ነገ አልን።
'ለቤቱ ህልውና አጥሩ ምኑ ነው! አልን። ያለንን ሁሉ ስንንቅ የተቃጣብን ኢላማ ቅጥሩን ያፈረሰ ”ለት፣ ሌላ ኢላማ ውስጥ ቀድሞ
የሚገባው ህልውናችን መሆኑ እንዴት ጠፋን?
ፍለጋ ከወጣሁ እኔ የተገኘ የሀሰትና የእውነት መልክ ይሄ ነው።
ከሀሰት በላይ፣ የእውነታዎች እሽቅድድም ቀዳሚውን እውነት አፋልሷል። ወደሮጡበት እውነት በትግዕስት መቆምን ያልቻሉ
ፍለጋዎችም በድንጋይ ላይ ድንጋይ” እንዲሉ፣ እርስ በእርስ ሲነባበሩ ትልቅ የሀሰት ኩይሳን ፈጠሩ። ከሀሰትና ከእውነታዎች ድቅል ያልተፈጠረ እኛነታችን የቱ ይሆን? ታሪካችን? ባህላችን? ፖለቲካችን?... ቀን የጣለ
“ለት፣ የወደደውን መልሶ ይጠላ ዘንድ እልፍ ምክንያት ሸሽጓልና፣ ፍቅራችን ሳይቀር ሌላ የንብብሮሽ ኩይሳ ነው።
ሲበዛ እራስ ወዳዶች ነን። ነገር ግን፣ ቅደም ተከተሉን የሳተ የአመክንዮ ድርድራችን ከፈጠረው የሀሰት ኩይሳ ተደግፈን ሳለን፣ በአንጻራዊ ስሌታችን ሀሰት እውነት ወደመሆን ባያድግም፣ ልክነትን ይፈጥራልና መሳታችንን ልብ አንልም።
ነገሩ የሚገባን ኩይሳችንን የጥፋት ውሀ ባገኛት ግዜ ነው።
“ይህ አንደኛው መሸነፍ ነው” አሉት።
Please login to view seller contact details.